You are currently browsing the Assimba Blog weblog archives for the day 20. December 2008.
| M | T | W | T | F | S | S |
|---|---|---|---|---|---|---|
| « Nov | Jan » | |||||
| 1 | 2 | 3 | 4 | 5 | 6 | 7 |
| 8 | 9 | 10 | 11 | 12 | 13 | 14 |
| 15 | 16 | 17 | 18 | 19 | 20 | 21 |
| 22 | 23 | 24 | 25 | 26 | 27 | 28 |
| 29 | 30 | 31 | ||||
- Articles (258)
- 22. January 2012: The Proxy Game
- 5. January 2012: Ato Bereket writes a book?
- 3. January 2012: I AM AN EaTHIOPIAN not Ethiopian
- 30. December 2011: GINBOT- 7 AND THE ETHIOPIAN FLAG ISSUE
- 23. December 2011: Change has to come to Ethiopia
- 17. December 2011: The 1976 TPLF Manifesto: TPLF’s “Republic of Greater Tigray”
- 11. November 2011: The Past is Prologue: Makonnen Araya (MA) - Master of Arts
- 11. November 2011: Why Ethiopians Must Unite: part four (a) of five. By Aklog Birara, PhD
- 1. November 2011: Why Ethiopians must unite Part three of five.
- 26. October 2011: Organization, Unity, and Leadership
Blogroll
- January 2012
- December 2011
- November 2011
- October 2011
- September 2011
- August 2011
- July 2011
- June 2011
- May 2011
- April 2011
- March 2011
- February 2011
- January 2011
- December 2010
- November 2010
- October 2010
- September 2010
- August 2010
- July 2010
- June 2010
- May 2010
- April 2010
- March 2010
- February 2010
- January 2010
- December 2009
- November 2009
- October 2009
- September 2009
- August 2009
- July 2009
- June 2009
- May 2009
- April 2009
- March 2009
- February 2009
- January 2009
- December 2008
- November 2008
- October 2008
- September 2008
- August 2008
- July 2008
- June 2008
- May 2008
- April 2008
- March 2008
- February 2008
- January 2008
- December 2007
Archive for 20. December 2008
በትግል ስም ትግልን መግደል - አ . ሰመረ
20. December 2008 by Assimba.
የአቶ ሰውየውን ጽሑፎች በዚህና በሌሎችም ድረ-ገጾች ላይ ስለሚያገኟቸው ያንብቡና እኒህ ወገናችን
በሚሉት ላይ በመጨመር ወይም በመደገፍ ካለያም የግል አስተያየትዎን ያስቀምጡልን
አቶ ሰውየው ከሕብረተ-ሰቡ የሚሰነዘረውን ለመስማት ዝግጁ ነው።
ነገሬን በተረት ልቀድሰው ባገራችን አንድ አባባል አለ ይኸውም ሰውየው ማንን ታሸንፋለህ ቢሉት ሚስቴን አለ ይባላል ደካማነቷን አይቶ ማለት ነው እንደሱ ያለውንና የፈረጠመውን ጎረምሳ እንዳይል ፈርቶ ይህንን አባባል እኛም ዛሬ ኢሀደግን እየታገልን ነው የምንለውም የዚ ተረት ወራሽ ሆነን እንደ ወረርሽኝ በሽታ ተዛምቶብን ዋናውንና የሀገራችን ደመኛ እህአዴግን ከመታገል ይልቅ አቅም ያጣውንና ሊያገግምና ሊነሳ የሚጣጣረውን የህዝብ ወገን የሆነውን ድጋፍ የሚሻውን ደካማውን እየፈለጉ ጭራሽ ከበሽታው እንዳያገግም በተኛበት ሄዶ እንዳይነሳ ማድረግ ጀግንነት አድርገነው ደረታችንን እንነፋለን ይሄ ጀግንነት ወይም ወንድነት አይደለም ይልቁንም ይሄንን መሰል ድርጊት ፈጻሚውን ትንሽነትና እርካሽነት የሚያሳይ ጉልህ መስታወት ነው።
በቅርቡ በተደጋጋሚ በተለያዩ ድህረገጾች ላይ አቶ ሰውየው በሚል ስም የግለሰቦችን ስም እያነሳ በጣም የወረደና ዝቅ ባለ ክብረነክ ዘለፋዎችን ጽፎ ተመልክቼ በጣም አዝኛለሁ። እኚህ ሰው ብዙ ግዜ በምገባባቸው የውይይት መድረኮች ውስጥ እድል ገጥሞኝ ስገባ አደምጣቸው ስለነበርና አመለካከታቸውም ከኔ ከግል አመለካከት ጋር በብዙ መንገዱ ስለሚቀራረብ ለኚህ ሰው ትልቅ ከበሬታ ነበረኝ። አሁን ድርጅት በድርጅት ላይ እየተፈጠረ ተቃዋሚው ቡድን ከቀን ወደቀን እየደከመ እየተከፋፈለ በመጣበት ጊዜ በመሀከላችን ያለውን ልዩነት ለማጥበብና ለመሰባሰብ ጎንበስ ቀና እያልን በምንሯሯጥበት ወቅት ተቃዋሚ ነን በሚል ስም በአድራጎት ግን ኢሀዴግን ሊያግዝ የሚችል ነገር እየሰሩ ተቃዋሚውን ካለው ድክመት ላይ ይባስ የሚያዳክም የእርስ በርስ ሽኩቻን አጋኖና አልፎም ተፈጠረ ለሚባለው አለመግባባት እንዳይበርድ እያራገቡ ያለ የሌለ ነገር እየቀባጠሩ መዘባረቅ የሚያስተዛዝብ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። አለመግባባት ካለም ላለመግባባት ምክንያት ለሆነው ጊዜ ሰጥቶ ለችግሩ መፍትሄ መሻት በተገባ ነበር ያን ሳያደርጉ ተንደርድሮና ተቻኩሎ ነገሩ እንዳይበርድ ተጣድፎ ለነደደው እሳት ቤንዚን ማቀበል እጅግ የሚያሳዝን አቀራረብ ነው። ምነው እኚህ ግለሰብ ለተፈጠረው አለመግባባት አስታራቂ ሊሆን የሚችል ሀሳብ እንዳሁኑ ለመከፋፈልና ለማዳከም እንደሮጡት ለማስታረቁም በዚሁ ፍጥነትና ጉልበት አልሰሩበትም? ለማፍረስና ለመከፋፈል ሲሆን ምን አጣደፋቸው? ለግንባታ ሳይሆን ለማፍረሱ ብእራቸው ሰላ እነኚህ ተወቃሾች ዛሬ ቢያንስ ኢህአዴግን ባለ አቅማቸው እየታገሉ ያሉ ግለሰቦች እንደሆኑ እኔ እንደግለሰብ የምመሰክርላቸው ብቻ ሳይሆን ማንም ስራቸውንና ድርጊታቸውን ያየ ሁሉ የሚመሰክርላቸው ነው። ነገር ግን የህዝብ ወገን እንደሆኑ እያወቅን እኛ ያልነው ብቻ ካልሆነ እኛን ካላደመጡ በሚል ትምክህት ተነሳስቶ ይህን ያክል ወቀሳና ክብረነክ ባልተገባ ነበር ። ዛሬ ባለንበት አገር የኑሮውን ሁኔታ እያወቅን ያንን ሁሉ መስዋእትነት ከፍለው እየታገሉ ያሉን ግለሰቦች እንደማበረታታት በተቃራኒው ከፍ ዝቅ እያደረጉ ማራከስና መዝለፍ ታጋዮች ከትግል እንዲርቁ ለማድረግ የሚደረግ የውስጥ ስራ ካልሆነ በስተቀር ሌላ ሊሆን ይችላል ብሎ ለመገመት ያዳግታል።
ኢህአዴግን በጠላትነት የፈረጀና ኢህአዴግን እታገላለሁ ከሚል አንድ ግለሰብ የሚጠበቅም አይደለምና ጸሀፊው ያላቸው አቋም ኢሀዴጋዊ እንጂ ኢትዮጵያዊና ወገናዊ አልመስል ብሎኛል።
ይህንን ተደጋጋሚ የሆነ ጽሁፍ ሲያወጡ በነገሩ አላሰቡበትም አልተጨነቁበትም ለማለትም አያስደፍርም ስለሆነም የኚህን ግለሰብ የፖለቲካ አመለካከት ቀደም ብዬ አደምጣቸው ከነበረውና ከአንደበታቸው ይወጣ ከነበረው ቃል ጋር እጅግ የተለየ ሆኖ በማየቴ እውን እኚህ ግለሰብ ያን ሁሉ ጊዜ ያልሆኑትን እንደሆኑ አድርገው ነበር የሚያቀርቡት? ያ ከሆነ በእውነት በማስመሰል ችሎታቸው ሳላደንቃቸው አላልፍም። ካልሆነ ግን መሰረተቢስ በሆነ የግል ፍላጎት ተነሳስቶ ዜጎችን ማዋረድ ባህላችን አይደለምና ጸሀፊው ልቦናው ሰጥቷቸው ወደህሊናቸው ተመልሰው ላደረጉት ስህተት ይቅርታ ጠይቀው ከትግሉ ጎራ ቢሰለፉ መልካም ነው የሚል አስተያየቴን እለግሳቸዋለሁ። ያን ማድረግ ቢያቅታቸው አንኳን ለሀገራቸው በሚደክሙና በሚለፉ ቡድኖችና ግለሰቦች መሀከል እየገቡ ቀና ሰዎችን እንዳይሰሩ ከማደናቀፍ ቢቆጠቡ ይመረጣል ይህንን መፈጸም ካልተቻላቸው ግን በትክክል ከየትኛው ወገን እንደሚያስፈርጃቸው ለጸሀፊው ልነግራቸው አይገባም ከኔ የላቁና ያወቁ ናቸው ብዬ አምናለሁና።
እዚህ ላይ አንድ ሳልጠቅሰው የማላልፈው ጉዳይ ቢኖር እኚህ ግለሰብ የሚደግፉት ድርጅት የሚወነጀልበት አንዱ ጸሀፊው በጽሁፋቸው የሚያንጸባርቁት አይነት የእኔ አውቅልሀልሁና የሁሉ ነገር ፈጣረና ወሳኝ እኛ ብቻ ነን የሚል ትምክህተኝነት ስለሆነ የሚወነጀሉበትን ሁኔታ ያጠናክረዋልና ምናልባት የሚደግፉትና እየታገልኩለት ነው ለሚሉት ድርጅት እውነተኛ ደጋፊው ከሆኑ ለድርጅታቸው አሳቢና ተቆርቋረ ከሆኑ ድርጅቱን እየጎዱት እንጂ እየጠቀሙት እንዳልሆነ እንዴት ተሳናቸው? ድርጅቱም የጸሀፊው አካሄድ ትክክል እንዳልሆነ አስገንዝቦ አቋም ሊወስድበትና አባላቱንም እንዲታረሙ ማድረግ የሚቻልበት መንገድ ካለ በጽሞና ሊያስብበት ይገባል።
በትግል ስም ትግልን ማዳከም በኢትዮጵያዊነት ስም ኢትዮጵያን መግደል በህዝብ ስም ህዝብን መበደል ሊያበቃ ይገባልና ወደ ህሊናችን ተመልሰን አገራችን ከወደቀችበት አዘቅት እናውጣት።
አ . ሰመረ
አድርባይና አስመሳይ ታጋዮች ይጋለጡ
ኢትዮጵያዊነት ለዘላለም ይኑር
አምላክ አገራችንን ይባርክልን
Posted in Articles | Print | 4 Comments »