እኔም ስለትብብር የምለው አለኝ

              ያትውልድ

ይህ አስተያየት እንድሰጥ ያነሳሳኝ አቶ ሲራክ ስለህብረት (ትብብር) ከ 1 እስከ 5 ያቀረበው አስተያየት ነው። በእርግጥ እኔም በከፊሉ እስማማለሁ። ቀሪው የማልስማማበት ሐሳቡ ላይ ግን ይህን አስተያየት ለመስጠት ተገድጃለሁ።

ወደ ህብረት ወይም ትብብር ጉዳይ ሀሳብ ከመስጠቴ በፊት እስኪ ስለ ትግሉና ትግል እናደርጋለን ስለሚሉ ድርጅቶች አላማ ልበል።

ላለፉት በተለየም 18 አመታት በጸረ ወያኔ ግንባር አያሌ የነጠላም የስብስብም ትግል ተካሂዶአል፤ በዚህ አውደ ውጊያ ብርቅ ድንቅ የሆኑ መልሰን ልናገኛቸው የማንችላቸው ነባር ታጋዮችን አጥተናል። ያም አሁን ላለው የተፋዘዘና እርስ በእርስ ያደበላለቀ ሁኔታ እንዲፈጠር አስተዋጸኦ አለው። በእርግጥ ነው ትግል በተናጠል ዛሬ ባለው ያገራችን ጭብጥ ሁኔታ የሚሆን ብንፈልግም የሚሳካ አይደለም በመሆኑም ይህችን አገር ከደመኛ ጠላታችን እጅ እንንጠቅ ካልን የድርጅቶች ማለትም ወያኔ ጠላት ነው መወገድ አለበት ብለው የሚያምኑ ሁሉ መስማማት ሲሆን መተባበር ካልሆነ ተከባብሮ ሳይጠላለፉ የጋራ ጠላት ላይ ማነጣጠር የሚጠበቅ ሁኔታው የሚያስገድደው ነው።

አቶ ሲራክ አምስት መስፈርቶች ለትብብር ወይም መፈጠር ላለበት ህብረት አቅርቦአል እነሱም 1-ያገሪቱን ሉአላዊነትና አንድነት የሚቀበሉ 2-እንደ AFD አይነት ጠላት ድርጅቶችን ያላቀፈ 3- ብቃት ያላቸው በግል መሬት የረገጡ መሆናቸው መታወቅ ያለበት 4- አስመሳይ ያልሆኑ 5- እወቁኝ ባይ ከሆኑ ለተክለ ሰውነት ከሚታገሉ መራቅ ይላል።

ከላይ ከሞላ ጎደል የተቀመጡት መስፈርቶች ያቶ ሲራክ ናቸው ታዲያ በእርግጥም ጠላት አንድ ብቻ ሳይሆን ጥንድ እንደሆነ ሊገጠም የሚገባውም በዚያው መልክ መሆኑን ይህ ጽሁፍ ያሳያል።

ጽሁፉ ውብ አቀራረብ እና መልካም እርእስ ከመያዙ በስተቀር እንደኔ አዲስ ነጻና ለየት ያለ እርእሱን የሚያግዝ ሀሳብ አልቀረበበትም ባይ ነኝ። ዛሬ በየፓልቶኩ ዘራፍ ሲባል የሚዋልበት ሀሳብ አልባ እና መረን ዘለል የሆኑ፤ ዛሬ ክበው ነገ ይሚያፈርሱ፤ ዛሬ አክብረው ነገ የሚያዋርዱ፤ ስለ ትግል ደንታ የሌላቸው ግለሰቦች ከዚህ የተለየ አላቀረቡም ያው እነሱ ሲሉት ሲደክሩበት የሚውሉትን ነው ሲራክም የደገመው። እንደኔ ሐሳብ ከሆነ ስለህብረት ወይም ስለትብብር ከማሰብ ከማለም በፊት ታጋይ ነኝ የሚል ግለሰብ፤ ስብስብ፤ ወይም ድርጅት ሁሉ የራሱን ህልም ተግባራዊ የሚያደርግበት ስልት ነድፎ ጠላትን በእውን የትግል አውድማ መፋለም መጀመር የግድ ይሆናል። ይህን ሳያደርግ ከተቀመጠበት ሳይነሳ ስለትብብር ማውራት ብቻውን ከወሬ ያለፈ አይሆንም። ተግባራዊ ቢሆን እንኩአን፤ የሚሰባሰቡት ያው መሰል ወረኞች ከመሆን ላይዘሉ ነው ባይ ነኝ።

ከላይ እንዳልሁት ዛሬ በየፓልቶኩ ስለ ትጥቅ ትግል ማውራት ወይም በትግል ስልት ልዩነት ፈጥሮ መነታረክ የተለመደ ሆኑአል። አንድ ጠበንጃ የተሸከመ ሰው ጫካ ሳይሰዱ ለምን ሰላማዊ ትግል አላችሁ ብለው ሲገለገሉ የሚውሉት ስንት ናቸው። የትናንት ቱባ ታጋዮች በስንቱ አፍ ተዘረጠጡ፤ ስንቱስ እነዚያን ብርቅየ ታጋዮችን አወገዘ? ያ ሁሉ የሚሆነው ዛሬ ባዲሱ ከኮምፒውተር ጀርባ ተቀምጦ በሚወራበት ፓልቶክ ነው። ዘንድሮም አምና ታች አምናም፤ እነዚያው ሰወች ስለትጥ፤ ስለህብረት፤ የጠላት አሰላለፍ ሲያወሩ ከርመዋል። ዛሬ ዛሬ አልፈው ተርፈው የዚህን የመነጋገሪያ መድረክ መቅለል ያዩ፤ መልከ መልካሞች የስደት መንግስት አዋጅ አውጀዋል። በነዚህ ሰወች መፍረድ የሚገባ አይመስለኝም። ስድቡንም ትናንት በታጋይነት ከሚያውቓቸው ዛሬ እርስ በእርስ ሲሰዳደቡ ያውም አይነት ያለው ስድብ ካፋቸው ሲወጣ አስተውለዋል። ባንድ አፍና ምላስ የስደት መንግስት ከመኝታ ክፍላቸው ሲያውጁ ከጥንት ታጋዮች መልስ ሲሰጥ ተመልክተዋል። እንግዲህ ያለንበትን ጊዜ ለማሳየት ስል የወዳጅ ጎራ የጠላት ጎራ ብሎ መከፋፈልም አስቸጋሪነቱን ለመጠቆም ነው ይኽን ያክል የምሽከረከረው። በእርግጥም አንድ ነገር መቀበል የግድ ይላል፡ ሁነኛ ታጋዮች ዛሬ እራሳቸው በፈጠሩት ችግር ተተብትበውና ተከፋፈለው ያሉበት ሁኔታ ነው የሚታየው። እንዴውም የዘመኑ በሽታ በነሱ የሚብስ ይመስላል። የነበራቸው ህብረተሰብን የመለወጥ ብርቅ ድንቅ ህልም ዛሬ በስድብና በመወነጃጀል ተለውጦ፤ ያጉል ተምሳሌ መሳለቂያ ለመሆን የቅድሚያ ቦታ ተይዞላቸዋል። ወደዋናው ጉዳይ ልመለስና፤ ላለፉት 18 አመታት ውብ ስራ የተሰሩትን ያክል ካንድ ህብረት ወደሌላ ሽግግር ግዜና ገንዘብ ያባከነ ይመስለኛል። ዛሬ ህብረት መፍጠር እንደዋነኛ የትግል ስልት በመቆጠሩ፤ በየትኛውም መታገያ እናምናለን የሚሉት ሜዳ ገብቶ ጠላትን ከመግጠም ይልቅ ከከተማ ከተማ መመላለስና ማን ከማን ይሆናል የሚለው ጎራ ልየታ በዋነኛነት በመያዙ ዋና ጠላት ተረስቶ፤ ፎክክሩ ቲፎዞ ማፍራት ሆኖአል። ይህ ለችግራችን አንዱ ይመስለኛል። ይህ ደግሞ ትንሽ ትልቅ ድርጅት ሳይለይ የተጠናወተን አቢይ ችግር ነው። አቶ ሲራክ እንዳለው AFD መቃወም መልካም ሆኖ ሳለ በምትኩ ግን ሊታይ ሊጨበጥ የሚችል ስራ ባለመደረጉ ካራት አመታት በሁአላም እዚያው ነን ማለት ነው። ዛሬ ስድብ ትግል፤ ትግልም ስድብ የሆነበት ጊዜ ነው። እንዴው ለላሙና ይህን የስድብ ጋጋታ ለማሳየት ከሁሉም በላይ አሳፋሪ ከሆኑት ትቂቶቹ “ እኔም ትግሬ ነኝ” በቤልጅግ አሊ “አለ ነገር በነብርቱካን መንደር” እነዚህን ለአብነት ለማሳየት እርእሶቹን ብቻ እንጅ ውስጠ ነገራቸው የሁለቱም ጽሁፎች አሳፋሪ አሳዛኝም እነዚያ ከጥንት ጀምረው ባረበኝነት በታገሉበት መድረክ ተራ የመንደር ተሳዳቢ ሲውረገረግበት ስናይ ባናዝን እናፍራለን ነው የሆነብን

እንግዲህ ህብረት ብቻውን የሚያመጣው ለውጥ ቢኖር ኢዴሐቅ፤ አማራጭ ሐይሎች፤ ሕብረት፤ ቅንጅት ከነዚያ በፊትም ፓሪስ 1፤ ፓሪስ 2 የተባሉ ነበሩን ግና ምን ፈየዱ ብለን ዛሬ ሒሳብ ልናወራርድ ብንነሳ የምናገኘው አወ በየጊዜው አዳዲስ የህዝብ ተስፋ ሰጥተዋል፤ ብሎም ትግሉን ግን ለድል ማብቃት አልቻሉም የሚል የሂሳብ ዘገባ ይኖረናል ማለት ነው። ለህብረት ምስረታ የታገልነውን ያክል እያንዳንዱ ድርጅት ቀበቶውን ጠበቅ አርጎ እና ኮስተር ብሎ በመሰለው ቢታገል ኖሮ ምናልባትም ካለንበት የተሻለ ሁኔታወች ቢአንስ ይኖሩን ነበር አልያም በለስ ቀንቶን ጠላትን ፈንግለነው ነበር። እንዳለ እድል ሆኖ ግን ቪዥን ያለው ከራሱ በላይ ለህብረተሰብ ለውጥ በቁርጥ የቆሙ መሪወች እያነሱ ወይም እየጠፉ መሄዳቸው ነው ይመስለኛል። ዛሬ ላለፉት አራት አመታት ድርጅቶች ከውስጥ እየፈረሱ ከሌላው ጋር ስለመተባበር ሲያወሩ ከርመዋል። ትግሉም ከላይ እንዳስቀመጥሁት፤ ወይዛዝርቱ ሳይቀር ከቆንጆ ቤታቸው ሳይወጡ መታገልን ስላወቁበት የስደት መንግስት እስከማቆቓም ደረሱ ማለት ነው። በዚያ ተቃውሞ የለኝም። ማንም ሰው ያሰበውን መስራት መብቱ ነው። ደግሞም አማራጭ ነው ብለው ሲያቀርቡ መልካም ቸር መንገድ ከማለት የሚያልፍ ትርፍ የሚያናግር ነገር የለውም። ግን የነዚህ ዜጎች ይህን ያክል እረጅም መንገድ ማሰብ ምክንያቱ እንደማነኛችንም ተስፋ ማጣት እና ባሉ መሪወችና ድርጅቶች እምነት መመንመን ይመስለኛ። ለዚህ ያደረሰን ደግሞ አቶ ሲራክ በየፈርጁ ያስቀመጠው ከማን እናብር የሚለው በውነቱ እንኩአን አቀበት አንድ እርምጃ ቁልቁል የሚሄድ አይመስለኝም። ለምን? ለሱ ጠላት እንደሱ የማያስብ ሁሉ መሆኑ ነው። እነሱ አንጃ ይሉታል እሱም አጃ ይላል። ግን ቃሉ እራሱ ያለፈበት ስለሆነ በጀ ብሎ የሚያዳምጥ ባለመኖሩ፤ እንደኔ ከሆነ የቁራ ጩኸት ሆኖ የቀረ ይመስለኛል። በሚኒሊክ ጊዜ የደነቆረ ይባል አይደል። ዛሬ ዘፈኑም እስክስታውም ስለተቀየረ እንደ አቶ ሲራክ አይነቶች ሁሉ የከበሮውን አመታት ቢቀይሩ ይሻላል ሰሚ ለማግኘት ነው ዋናው ነገሬ።

ታዲያ የሲራክን አስተሳሰብ መንቀፌ መተባበር አያስፈልግም ለማለት ሳይሆን፤ 1- መተባበር አስፈላጊ ነው ግን ለትብብር ቅድመ ሁኔታ ተገቢ አይደለም 2- ዛሬ ጠላታችን አንድ ብቻ ሆኖ የዚህ ጠላት ጥንካሬ ደግሞ በተቃዋሚ ጎራ ያለው አለመስማማት በመሆኑ፤ እንደኔ ይህ መጭው ትግል መለኝነትን፤ መሰሪነትን የሚፈለግ ነው፤ ስለሆነም ማንም የዚህ ደመኛ ጠላትን መወገድ የሚያምን ሁሉ ከኦጋዴን እንስከ ኢሮብ፤ ከሰላማውያኑ ታጋዮች እስከ ታጣቂወች ቢቻል ባንድ የትብብር ጃንጥላ አልያም ላለመነካካት ተስማምቶና ተከባብሮ በጠላት ላይ ፊትን ማዞር ምርጫ የሌለው ነው ብየ አምናለሁ። ይህ ነው ከሲራክ ጋር የማያስማማኝ እንዴውም የሲራክ አስተሳሰብ የመሸበት እና ለጠላት ጠቃሚ በመሆኑ ደግሞ ይታሰብበት ባይ ነኝ።

ያትውልድ

This entry was posted in Articles. Bookmark the permalink.

8 Responses to እኔም ስለትብብር የምለው አለኝ

  1. Geremew Kinde says:

    The writer seems confused and his message is obscure.What is his problem with Beljig Ali’s article? Is he saying there is no anja these days? I hsave failed to grasp the essence of his precouupation or direction.Maybe he should be bold enough to write clearly.

  2. Meseret Alemu says:

    I found the article of Sirak well written and objective while this one sounds half Weyane and half Eprp anja.Why does he call himself ya tiwld as he is obviouslt not from that generation.

  3. Meseret Alemu says:

    The comment on the woman who formed the sidet mengist is proper but Ya Tiwld sounds anja.Let him leave that stupid group to get his sanity back

  4. Meseret Alemu says:

    Ya Tiwld has not understood Sirak properly.Ya Tiwld comes out confused big time because he is obviously a follower of anja old man Mersha and he is trying to shout their position.That Harar Werk attacks him is good–at least he has said one thing right. Ya Tiwld needs to rethink hios position.

  5. Almaz Werku says:

    Meseret thank you for your comments but Ya Tiwld has also raised some serious issues we should discuss.Maybe he is anja follower and his view may be affected by that but his criticis of Sirak can provoke us to discuss the main issue of front.What is Timret?What is the broad front being propagated by the Mersha group vis their radio? The criticism of the Dallas woman is also good as Dr.Abeba also supports the idea of a sidet mengist in her pal talk.

  6. Hamid Hussein says:

    Ya Tiwld has raised some points of interest though his crtitc of Sirak is weak and mistaken. The UEDF was sabotaged by Liodetu and Berhanu Mega and others.Kinjit itself got the same poison.EPRP made mistake of unitign with Meisone and Aregawi and Ayalsew who have few members and with Derje who is TPLF spy. Ya Tiwld seems symapthiser of Ato Mersha whose radio in DC and the pal talk of weekend show his line is very very bad. Unity with Lencho? with Berhanu? Ya Tiwld is with bad crowd and his idea is therefore as bad

  7. Tokichaw says:

    The write appear to have no any motive other than taking the opportunity to undermine the article “enem tigre neg”and to attack the writer as well .Because ato sewyw i strongly feel he is an outspoken person who calls a spade a spade.I think ato sewyew should up keep his firm stand against these riff-raff anjas of prospective woyanes.

Comments are closed.